በረሃማና ከፍተኛ የውሃ እጥረት ያለባቸው አካባቢዎችን ለማልማት የሚያስችሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሀገር ውስጥ የማስገባት ሂደት በቅርቡ ይጀመራል።

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ አሀመዲን መሃመድ (ፒ ኤች ዲ) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ከተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ከፍተኛ የአየር ንብረት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር ተወያይቷል።

በውይይቱ ዩናይትድ አረብ ኢሚሬትስ በረሃማ ቦታዎችን ያለማችበትን መንገድና የቴክኖሎጂ የልምድ ልውውጥ ተደርጓል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ አህመዲን መሃመድ (ፒ ኤች ዲ) በቅርብ ጊዜ ውስጥ ቆላማና በረሃማ የሆኑ አካባቢዎች ለማልማት የሙከራ ስራዎችን ለመስራት አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን፣ ባለሙያዎችን እና መሳሪያዎችን ወደ አገር ውስጥ የማስገባት ሂደት ይጀመራል ብለዋል።

በሚኒስትር ዴኤታው የተመራው ቡድን ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት፣ ከብሄራዊ ሜትሮሎጂ ኤጀንሲ፣ ከተፋሰስ ባለስልጣን፣ ከሰው ሰራሽ አስተውሎ ማዕከል፣ ከቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት፣ ከኢንፎርሜን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ እና ከስፔስ ሳይንስ ኢንስቲትዩት የተውጣጡ የስራ ኃላፊዎችን የያዘ ነው።

ይህንን ልጥፍ ያጋሩ

Share on twitter
Share on linkedin
Share on facebook