የዜጎች ቻርተር

ራዕይ

መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ የኦንላይን አገልግሎቶችንና መረጃዎችን ለማቀበል ድልድይ በመሆን በተጠቃሚዎች ቀዳሚ የሆነ ምርጫ መሆን።

  • ሁሉንምየሚኒስቴር መ/ቤቱን አገልግሎቶች በአንድ መስኮት አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል፡፡
  • ለተጠቃሚዎች የመረጃና የግብይት አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ ሁኔታ መስጠት ማስቻል፡፡
  • መንግስትያቀደውን የ5 ዓመቱን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ እንዲሳካ ለማስቻል የመረጃ ቅብብሎሹን ማፋጠን፡፡

ተግባር

  • በቀን የ24 ሰዓት በሳምንት ሰባት ቀናት አገልግሎት ማግኘት ማስቻል
  • በውይይት መድረኮችና ብሎጎች/ጡመሮች በመጠቀም ዜጎች፣ የንግዱ ማህበረሰብና ሌሎች ተጠቃሚዎች የሚኒስቴር መ/ቤቱ ጉዳዮችና ፖሊሲዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማስቻል፡፡

ሚኒስቴር መ/ቤታችን

  • የመረጃ ቅብብልን ለማቃለል በየቀኑ እየተጋ ይገኛል እዚህ የመረጃ ፖርታል ላይ ያቀረበው መረጃ መቶ በመቶ ትክክለኛና ወቅታዊ ነው ብለን ማረጋገጥ አንችልም፡፡ በእዚህ ፖርታል ላይ ወቅታዊ ያልሆነ ወይንም የተለወጠ አልያም የተሳሳተ መረጃ ካገኙ ከዚህ በታች በተሰጠው አድራሻ እንዲያሳውቁን በትህትና እንጠይቃለን፡፡